Teneta Dessie Zuria

Teneta Dessie Zuria Yimam Seid

17/09/2025
ቆቦ‼ቆቦ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ውስጥ በደንብ መተላለፍ ተይዘው የነበሩ 48 የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች ህውሃት ከተማዋን በወረረበት ወቅት ተዘርፈው ተወስደው ነበር።ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ በክትት...
19/08/2022

ቆቦ‼

ቆቦ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ውስጥ በደንብ መተላለፍ ተይዘው የነበሩ 48 የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች ህውሃት ከተማዋን በወረረበት ወቅት ተዘርፈው ተወስደው ነበር።ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ በክትትል ተደርሶበት ከእነሰሌዳዎቹ ከጥሬ ገንዘብ ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉን የቆቦ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ታደሰ ተሰሜ ገልፀዋል ሲል የተማዋ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

‟ከወልቃይት ጠገዴ ወንድሞቻችን ጋር የሚያገናኘን የአሥፓልት መንገድ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረግን ነው” የአጅሬ ጃኖራ ነዋሪዎችደባርቅ፡ ነሐሴ 06/2014 ዓ.ም ...
17/08/2022

‟ከወልቃይት ጠገዴ ወንድሞቻችን ጋር የሚያገናኘን የአሥፓልት መንገድ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረግን ነው” የአጅሬ ጃኖራ ነዋሪዎች

ደባርቅ፡ ነሐሴ 06/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በሰሜን ጎንደር ዞን እየሠራቸው ከሚገኙ መንገዶች መካከል ከዳባት - አጅሬ - ጠገዴና ማክሰኞ ገበያ እየተሠራ የሚገኘው የአሥፓልት መንገድ ተጠቃሽ ነው።

99 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህ የአሥፓልት መንገድ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ከዳባት - አጅሬ - ጠገዴና ማክሰኞ ገበያ ከሁለት ተከፍሎ ፓወር ኮን በተባለ ተቋራጭ እየተሠራ ይገኛል። መንገዱ ለአካባቢው ማኅበረሰብ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን የሚሰጥ ነው።

በዳባት ወረዳ የአጅሬ ጃኖራ አካባቢ ነዋሪው አቶ ማሙሽ ከፍያለው "የመንገድ አለመኖር እናቶች በወሊድ ምክንያት በመንገድ ላይ እንዲቀሩ፤ ምርት ለገበያ እንዳይቀርብ፤ ከሌሎች ወገኖቻችን ጋር በክፉም በደጉም እንዳንገናኝ አድርጎን ቆይቷል"ብለዋል።

የአሥፓልት መንገዱ ሲጠናቀቅ የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ ተጠቃሚ ስለሚያደርጋቸው ለመንገድ ሥራው ድጋፍ እያደረጉ እንደኾነ አስረድተዋል።

አቶ ረዲ ዳውድ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው መንገዱ ብዙ መስዋእትነት ተከፍሎ ወደ ቀደመ ማንነቱ ከተመለሰው የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ኅብረተሰብ ጋር የሚያገናኝ መኾኑ ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው ብለዋል። የመሬት ካሣ ክፍያዎችም በጊዜ እንዲፈጸሙ ጠይቀዋል፡፡

የዳባት አጅሬ ጠገዴና ቅራቅር አሥፓልት መንገድ ፕሮጀክት ሥራ አሥኪያጅ አዲሱ ጌታሁን፤ የአሥፓልት መንገድ ሥራውን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እያደረጉ መኾናቸውን ገልጸው የመንገድ ቆረጣና የማገናኘት ሥራው 80 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል።

የሲሚንቶና የነዳጅ እጥረት ለሥራው ማነቆ እንደኾነባቸው የጠቆሙት ሥራ አሥኪያጁ መንግሥት ችግሮቹን ለመቅረፍ ጥረት እያደረገ በመኾኑ የአሥፓልት መንገድ ሥራውን በ2016 ዓ.ም ለማጠናቀቅ እየሠሩ መኾናቸውን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የፕሮጀክቱ አማካሪ ግርማ ነጋሽ "ሀገሪቱ ባለችበት ወቅታዊ ሁኔታ የመሬት ካሣ ክፍያዎች ቢጓተቱም መንግሥት በሂደት ክፍያውን እየፈጸመ ነው” ብለዋል። ለመንገድ ሥራው የማኅበረሰቡ ተሳትፎ እገዛ እያደረገ እንደኾነም አስረድተዋል።

የዳባት ወረዳ አሥተዳዳሪ ገብረሕይወት መኳንንት የአሥፓልት መንገድ ሥራውን በቅርበት እንደሚከታተሉ ገልጸው አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ከማኅበረሰቡ ጋር በመወያየት ለሥራው እንቅፋት የሚኾኑ ችግሮችን እየፈቱ ሥራው እንዲቀጥል እያደረጉ መኾናቸውን ገልጸዋል።

የአሥፓልት መንገድ ሥራው ሲጠናቀቅ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ለረጅም ዓመታት ለያይቶ እንዳይገናኝ ካደረገው የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ጋር በማገናኘት ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር ለመፍጠር እንደሚያስችል ነው የገለጹት።

ዘጋቢ፡- አድኖ ማርቆስ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን‼

ከእኛ ጋር ስለኾኑ እናመሰግናለን‼

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/

"የትምህርት ባለሙያዎች በጠንካራ ሥነ ልቦና የታነጸና በሥነ ምግባር የበለጸገ ትውልድ ልትፈጥሩ ይገባል" ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ።ሑመራ፡ ነሐ...
17/08/2022

"የትምህርት ባለሙያዎች በጠንካራ ሥነ ልቦና የታነጸና በሥነ ምግባር የበለጸገ ትውልድ ልትፈጥሩ ይገባል" ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ።

ሑመራ፡ ነሐሴ 10/2014 (አሚኮ) በአማራ ክልል ትምሕርት ቢሮ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ትምሕርት መምሪያ የ2014 ዓ.ም የሥራ አፈጻጻም እና የ2015 ዓ.ም የትምሕርት ዘመን የንቅናቄ መድረክ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በሑመራ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩም የ2014 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2015 ዓ.ም እቅድ ቀርቦ ከትምህርት ባለሙያዎችና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው፤ የሀገር ኢኮኖሚ የሚገነባው በተማረ የሰው ኀይል በመኾኑ በዕውቀት የተካነ እና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ልትሠሩ ይገባል ብለዋል።

የዞኑ ማኅበረሰብ ለበርካታ ዓመታት ባሕልና እሴቱን ፣ ቋንቋና ታሪኩን ተነጥቆ የነበረ ሕዝብ በመኾኑ ኅብረተሰቡ ባሕልና ቋንቋውን እንዲያዳብር በትምህርቱ ዘርፍ መሥራት ይገባል ነው ያሉት።

አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በከፈተው ጦርነት ምክንያት በዞኑ ከ105 ሺህ በላይ መጽሐፍቶች ፣ ከ10 ሺህ በላይ የትምህርት ቤት ወንበሮች ፣ ከ600 በላይ የሥራ ማስኬጃ ኮምፒዩተሮች ፣ ከ1ሺህ 400 በላይ ሰሌዳዎች መውደም ፣ የበጀት አለመኖር እና ከዞን ትምህርት መምሪያ እስከ ትምህርት ቤቶች የባለሙያ እጥረት እና ያሉ ባለሙያዎችም ያለባቸው የልምድ ማነስ በዞኑ የትምህርት አሰጣጥ ሂደት ላይ ጫና ማሳደሩ ተጠቅሷል።

ከነፃነት ማግስት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ትምህርት መምሪያ በአዲስ በመዋቀር በዞኑ ካሉ 197 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና 23 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 132 አንደኛ ደረጃ እና 21 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ወደ ሥራ አስገብቷል።
ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ እንዳይርቁና በቂ እውቀት እንዲሸምቱ ባለሙያዎች የበጀት አለመኖርና የግብዓቶች አለመሟላት ሳይገድባቸው ተማሪዎችን በዕውቀት ብቁ ለማድረግ መትጋታቸው በጠንካራ ጎን ተነስቷል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ተማሪዎች በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲኾኑ በዞኑ የመጽሐፍ እጥረት እንዲቀረፍ ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች ለትምህርት ተቋማት ትኩረት ሰጥተው ድጋፍ እንዲያደርጉ ፣ የ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በታቀደለት ጊዜ እንዲጀመር እና ተማሪዎች በወቅቱ እንዲመዘገቡ ከማኅበረሰቡ ጋር የንቅናቄ መድረክ እንዲፈጠር ጠይቀዋል።

ከውይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ገብረ ማርያም መንግስቴ በዞኑ የወደሙ ትምህርት ቤቶችንና የትምህርት መስጫ ግብዓቶችን ለማሟላት ከአማራ ክልል ትምህርት ቢሮና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየተሠራ ነው ብለዋል።
የትምህርት ጥራት እንዲረጋገጥና ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንዲችሉ ኀላፊነትን መወጣት ይገባል ያሉት የመምሪያው ኀላፊ በ2015 ዓ.ም በቁሳቁስ እጥረትና በሰው ኀይል አለመሟላት የተዘጉ 67 ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት እየተሠራ ነው ብለዋል።
በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን የመማሪያ መጽሐፍ ሙሉ በሙሉ ለማሟላት ከክልሉ ትምህርት ቢሮና ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየተሠራ መኾኑንም ተናግረዋል።

አስተማሪ ያልቀረጸው ትውልድ ሀገርን መገንባት አይችልምና የትምህርት ባለሙያዎች በስነ ልቦና የነቃና በስነ ምግባር የበለጸገ ትውልድ ልትፈጥሩ ይገባል ያሉት የዞኑ ምክትል አሥተዳዳሪ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ዞኑ ለትምህርት ተቋማት ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል

ሰውየው በጎመን ጠቅልሎ ሲያዘዋውር የነበረ የጥይት ካዝና ተይዟልትናንት ከኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ በሰማነው መረጃ በከተማው ማናኸሪያ 60 የጥይት ካዝና በጎመን ተጠቅል...
17/08/2022

ሰውየው በጎመን ጠቅልሎ ሲያዘዋውር የነበረ የጥይት ካዝና ተይዟል

ትናንት ከኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ በሰማነው መረጃ በከተማው ማናኸሪያ 60 የጥይት ካዝና በጎመን ተጠቅልሎ ለጥፋት ዓለማ በህገወጥ መንገድ ለማዘዋወር ሲሞከር በህበረተሰብ ጥቆማ ተይዟል።

ከጠዋቱ 5 ሰዓት አከባቢ ከሲዳማ ክልል ፤ ጩኮ አከባቢ የተነሳ አንድ ግለሰብ በ3 እስር ጎመን ውስጥ በመደበቅ ለጥፋት አካላት ሊደርሰው የነበረ 60 የጥይት ካርታ በቁጥጥር ስር ውሏል።

ጥግ የደረሰ ሞኝነት

ለታማኙ ወጣት ዕውቅና እና ሽልማት ተበረከተለት፡፡ ደሴ: ነሐሴ 09/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በደሴ ከተማ  በሚያሽከረክረው ታክሲ ላይ በተሳፋሪ የተረሳን 16 ሺህ ብር ለባለቤቱ አፈላልጎ የመለ...
16/08/2022

ለታማኙ ወጣት ዕውቅና እና ሽልማት ተበረከተለት፡፡

ደሴ: ነሐሴ 09/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በደሴ ከተማ በሚያሽከረክረው ታክሲ ላይ በተሳፋሪ የተረሳን 16 ሺህ ብር ለባለቤቱ አፈላልጎ የመለሰው ወጣት ኤርሚያስ ባዬ ዕውቅናና ሽልማት ተበረከተለት፡፡

ነሐሴ 7/2014 ዓ.ም ደሴ ከተማ ታክሲ እያሽከረከረ የዕለት ከዕለት ሥራውን እያከናወነ ሳለ ጋቢና ላይ ገንዘብ ረስተው የወረዱትን እናት በማፈላለግ ገንዘባቸውን ያስረከበው ወጣት ኤርሚያስን በተመለከተ አሚኮ ዘገባ መሥራቱ ይታወሳል፡፡

የደሴ ከተማ አሥተዳደር ለወጣቱ 10 ሺህ ብር እና የምስክር ወረቀት አበርክቶለታል፡፡

የደሴ ከተማ አሥተዳደር ምክትል ከንቲባ ሱሌማን እሸቱ እንዳሉት የወጣት ኤርሚያስ በጎነት የመልካም እሴት መገለጫ ነው። በቀጣይ ወጣት ኤርሚያስን የደሴ ከተማ የወጣቶች የበጎነት ተግባር አምባሳደር በማድረግ አብረን እንሠራለን ብለዋል።

የደሴ ከተማ አሥተዳደር ብልጽግና ፖርቲ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አቶ ሞላ ሁሴን እንደገለጹት ወጣት ኤርሚያስ የሕዝብን የቆየ ባሕልና ወግ በማሳየቱ ከልብ እያመሰገንን ወደፊት በተለያዩ የልማት ሥራዎች ላይ አምባሳደር አድርገን እንሠራለን ነው ያሉት።

ባሕር ዳር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከደረጃ 1 እሰከ ደረጃ 5 ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ። ባሕር ዳር: ሐምሌ 24/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ባሕር ዳር  ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቀንና በማታ መርኃ...
04/08/2022

ባሕር ዳር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከደረጃ 1 እሰከ ደረጃ 5 ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

ባሕር ዳር: ሐምሌ 24/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ባሕር ዳር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቀንና በማታ መርኃግብር ሲያሰለጥናቸው የነበሩ 1 ሺህ 471 ሰልጣኞችን ዛሬ አስመርቋል።

ከተመራቂዎች መካከል 685ቱ ሴቶች ናቸው።
ኮሌጁ በ14 የትምህርት ክፍሎች እና በ65 የሙያ ዘርፎች እንደሚያሰለጥን ነው የተገለጸው።

የባሕር ዳር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ፈለቀ ውቤ እንዳሉት ተመራቂዎች ፈተናዎችን ተቋቁማችሁ ለዚህ ቀን በመብቃታችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ።

ኮሌጁ በተከታታይና በአጫጭር ሥልጠና መርኃግብሮች እያሰለጠነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ኮሌጁ በአጫጭር እና በተከታታይ ሥልጠናዎች በግብርና፣ በኢንዱስትሪ ልማት፣ በብረታብረት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በሆቴልና ቱሪዝም እንዲሁም በሌሎችም የሙያ መስኮች ሥልጠና ይሰጣል ብለዋል።

የኮሌጁ ዲን ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክትም "በትምህርት ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር የሥራ ፈጠራ ተግባራት ላይ የምትሰማሩ፣ ሕዝብንና ራሳችሁንም የምትጠቅሙ እንድትኾኑ አደራ እላችኋለሁ" ብለዋቸዋል።

የአማራ ክልል ሥራና ሥልጠና ምክትል ቢሮ ኃላፊ አማረ ዓለሙ ተመራቂ ተማሪዎች በተማራችሁት ትምህርት የሀገራችሁ ችግር ፈች መኾን ይገባችኋል ነው ያሉት።

የወሰዳችሁት ሥልጠና በአመለካከትም፣ በዕውቀትና በክህሎትም ሥራን ፈጥሮ ለመሥራት የሚያስችል በመኾኑ በሙያችሁ ራሳችሁንና ሀገርን የምትጠቅሙበት መኾን ይገባል ነው ያሉት።

ዘጋቢ:- ጋሻው አደመ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን‼

ከእኛ ጋር ስለኾኑ እናመሰግናለን‼

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J

በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/

አቶ ደመቀ መኮንን ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ጋር ተወያዩ።ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮ...
26/07/2022

አቶ ደመቀ መኮንን ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ጋር ተወያዩ።

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ጋር ተመካክረዋል፡፡

ምክክሩ በግንቦት ወር በጄኔቫ የተካሄደውን ውይይት ተከትሎ የተደረገ ነው ተብሏል፡፡

ባለሙያዎቹ ከመንግስት ባለስልጣናትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተው የተሰጣቸውን ተልዕኮ በመወጣት ከመንግስት ጋር በጋራ መፍትሄ ለመፈለግ አዲስ አበባ መገኘታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለተወያዩ።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን‼

ከእኛ ጋር ስለኾኑ እናመሰግናለን‼

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/

ሕጋዊ ያልሆኑ የትምሕርት ተቋማት ላይ ጥብቅ እርምጃ እየወሰደ መኾኑን የትምሕርትና ሥልጠና ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡አዲስ አበባ፡ ሐምሌ 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ ሕገ ወጥ   የትም...
26/07/2022

ሕጋዊ ያልሆኑ የትምሕርት ተቋማት ላይ ጥብቅ እርምጃ እየወሰደ መኾኑን የትምሕርትና ሥልጠና ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፡ ሐምሌ 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ ሕገ ወጥ የትምሕርት ተቋማት መስፋፋት የትምሕርት ጥራት ጥያቄ ዉስጥ እዲወድቅ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ ነዉ ሲሉ የኢፌዴሪ የትምሕርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አንዱዓለም አድማሴ (ዶ.ር) አስታወቁ፡፡

በ2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተደረገ የመጀመሪያ ዙር የተቋማት ፍተሻ ከ147 ተቋማት ዉስጥ በ 106 የትምሕርት ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን አስታውቀዋል፡፡ በሁለተኛ ዙር በክልሎች ባሉ የትምሕርት ተቋማት በተደረገ ፍተሻ ደግሞ በ 95 ተቋማት ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተናግረዋል፡፡

ትዉልድን በመቅረጽ እና ሀገርን በመገንባት ሂደት የትምሕርትን ሚና የሚያክለዉ እንደሌለ የዘርፉ ተመራማሪዎች ያስረዳሉ፡፡ በዚህ ሂደት የትምሕርት ሚና ትርጉም የሚኖረዉ ግን ጥራቱን የጠበቀ ከኾነ ብቻ ነዉ ብለዋል፡፡

ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢፌዴሪ የትምሕርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንዱዓለም አድማሴ፤ አሁን ላይ የትምሕርት ጥራት በኢትዮጵያ ጥያቄ ዉስጥ የገባበትን ሁኔታ አብራርተዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ኀላፊነት የማይሰማቸዉ እና ትርፍን ብቻ ዒላማ ያደረጉ ሕገወጥ የግል የትምሕርት ተቋማት መስፋፋት ምክንያት እንደኾኑ ጠቅሰዋል፡፡

መንግሥት የትምሕርት ጥራትን ለማስጠበቅ እየወሰዳቸዉ ካሉ ተጨባጭ እርምጃዎች ሕገ ወጥ የትምሕርት ተቋማትን መቆጣጠር አንዱ ተግባር እንደኾነ ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡

ፈቃድ ሳያገኙ ትዉልድን እያቀጨጩ እና የምስኪኑን አርሶ አደር ኢኮኖሚ ክፉኛ እየጎዱ ያሉ ሕገ ወጥ የግል ከፍተኛ የትምሕርት ተቋማትን ለመቆጣጠር በሚደረገዉ ሂደት ኅብረተሰቡ ንቁ ተሳታፊ እንዲኾን አስገንዝብዋል፡፡

ኅብረተሰቡ ስለተቋማት ሕጋዊነት በ9799 ነጻ የስልክ ቁጥር ደዉሎ ማረጋገጥ እንደሚገባ ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ዘጋቢ፡-በለጠ ታረቀኝ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን‼

ከእኛ ጋር ስለኾኑ እናመሰግናለን‼

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/

Address

0921638790
Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Teneta Dessie Zuria posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category