Peps or coca

Peps or coca Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Peps or coca, Grocers, Hawassa, Awassa.

06/09/2024
24/07/2024

በቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳና መሰንጠቅ 208 ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል።

እንደ ዞን ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በከፍተኛ አደጋ ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውም ተገልጿል።

የቤንች ሸኮ ዞን ግብርና ፣ ደን ፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ ማምሻውን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የክረምቱ የዝናብ መጠን መጨመር ጋር ተያይዞ በሰሜን ቤንች ወረዳ ቃሻ ፣ ሙያ ኬላና ዋላ ቀበሌዎች ከፍተኛ የሆነ የመሬት መሰንጠቅና ናዳ መከሰቱን ገልጸዋል።

ትላንት ማምሻውንና ዛሬን ጨምሮ በ3 ቀበሌዎች ሰሞኑን በተከታታይ በጣለው ዝናብ 28 የመኖሪያ ቤቶች የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ደርሶባቸዋል ብለዋል። እንዲሁም በቀበሌዎቹ የበቆሎ ፣ እንሰት ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ማሳዎች በናዳው መውደማቸውን ገልጸዋል። እስካሁን 208 ለአደጋ ተጋላጭ ሰዎችን ከስፍራው በማውጣት በቀሌዎች ግቢ ፣ በቤተክርስቲያንና ወደ ዘመዶቻቸው የማዘዋወር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።

እንደ ብሔራዊ ሜትሮሎጂ አገልግሎት መረጃ ከሆነ በቀጣይም በቀጠናው ከባድና ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል በትንበያ መግለጹን የጠቆሙት ኃላፊው የዝናብ መጠኑ የሚቀጥል ከሆኑ በወረዳው ተጨማሪ 4 ቀበሌዎች በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገቡ ጠቁመዋል።

ዋላ ቀበሌ አካባቢ ከዋቻ ማጂ - ማጂ በሚወስደው የአስፓልት መንገድ ላይ የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ተከስቷል ያሉት አቶ መስፍን የሚመለከታቸው አካላት በፍጥነት የጥገና ስራ ካለሰሩ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ሊቋረጥ እንደሚችል ገልጸዋል።

ነገ ከዞኑ የተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው እንደሚጓዝ አቶ መስፍን ጠቁመው የባለሙያዎች ሪፖርትን መሰረት አድርጎ የዞኑ መንግስት ጊዜያዊና ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ ይመክራል ብለዋል።

እንደ ዞን ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በቅጽበታዊ ጎርፍ መጥለቅለቅ ፣ የመሬት መሰንጠቅና የናዳ ችግር ውስጥ መሆናቸውን በመግለጫቸው የጠቆሙት አቶ መስፍን በተለይ ሚዛን አማን ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

እስካሁን በሰውና በእንሳት ላይ የደረሰ አደጋ አለመኖሩን ኃላፊው ጠቁመው በሰሜን ቤንች ወረዳ ተጋላጭ በሆኑ 7 ቀበሌዎች ህጻናት ወደ ማሳ እንዳይሄዱ ማድረግ ፣ አርሶ አደሩም እንስሳትን ወደ ግጦሽ ይዞ እንዳይሄድ የቅስቀሳና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተሰራ መሆኑን በጋዜጣዊ መግለጫቸው ጠቁመዋል ሲል የቤንች ሸኮ ኮሙኒኬሽን ዘገባ ተመልክተናል።

ጎፋ ከአደጋው ማግሥት ጎፋ፦በመሬት መንሸራተት አደጋው በአሁኑ ወቅት ከ40 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከአፈር በታች ይገኛሉ የሚል ጥርጣሬ መኖሩን የገዜ ጎፋ ወረዳ ባለሥልጣናት ዐሳውቀዋል ።ከትናንት...
24/07/2024

ጎፋ ከአደጋው ማግሥት

ጎፋ፦በመሬት መንሸራተት አደጋው በአሁኑ ወቅት ከ40 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከአፈር በታች ይገኛሉ የሚል ጥርጣሬ መኖሩን የገዜ ጎፋ ወረዳ ባለሥልጣናት ዐሳውቀዋል ።

ከትናንት በስቲያ ሰኞ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ 16 የቤተሰብ አባላቱን ያጣ፤ አምስት የባለቤታቸው ቤተሰብ አባላትን የቀበሩም አሉ።

አደጋውን አስከፊና በቃላት ለመግለጽ እንደሚከብድ የተናገሩት አቶ ዘለቀ « የቤተሰብ አባሎቻቸውን ከአፈር ናዳ ሥር ለማግኘት ያለውን ፈተና ከባድና የሚጨንቅ ነው ብለዋል።

ከተጫነው ናዳ ሥር የወጡ ሟቾች በጭቃ የተለወሱ ናቸው ። ሰዎች የቤተሰብ አባሎቻቸውን የሚለዩት የአስክሬኖችን ፊት በማጠብ ነው።

16 የቤተሰብ አባላቱን ያጣ ፣ ስምንት ልጆቿን ያጣች እናት አለች ፣ ቤተሰቦቹ አልቀውበት ብቻው የቀረ ሕጻንም አለ ፡፡ ሁኔታው ዘግናኝና አስጨናቂ ነው» ብለዋል ። በቀበሌው የደረሰው አደጋ ቁጥሩ ቢለያይም እያንዳንዱን ቤት ለከፋ ኃዘን መዳረጉን ተጎጂዎች ለዶቹ ቬለ ተናግረዋል ።

በመሬት መንሸራተት አደጋው ሕይወታቸው ያለፈ ቀሪ ሰዎችን የመፈለጉ ሂደት አሁንም መቀጠሉን የወረዳ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ማስረሻ ማንአየ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።

ሸዋንግዛው ወጋየሁ ዶቸ ቬለ

በቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳና መሰንጠቅ 208 ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል።  እንደ ዞን ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በከፍተኛ አደጋ ውስጥ የ...
24/07/2024

በቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳና መሰንጠቅ 208 ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል።

እንደ ዞን ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በከፍተኛ አደጋ ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውም ተገልጿል።

የቤንች ሸኮ ዞን ግብርና ፣ ደን ፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ ማምሻውን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የክረምቱ የዝናብ መጠን መጨመር ጋር ተያይዞ በሰሜን ቤንች ወረዳ ቃሻ ፣ ሙያ ኬላና ዋላ ቀበሌዎች ከፍተኛ የሆነ የመሬት መሰንጠቅና ናዳ መከሰቱን ገልጸዋል።

ትላንት ማምሻውንና ዛሬን ጨምሮ በ3 ቀበሌዎች ሰሞኑን በተከታታይ በጣለው ዝናብ 28 የመኖሪያ ቤቶች የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ደርሶባቸዋል ብለዋል። እንዲሁም በቀበሌዎቹ የበቆሎ ፣ እንሰት ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ማሳዎች በናዳው መውደማቸውን ገልጸዋል። እስካሁን 208 ለአደጋ ተጋላጭ ሰዎችን ከስፍራው በማውጣት በቀሌዎች ግቢ ፣ በቤተክርስቲያንና ወደ ዘመዶቻቸው የማዘዋወር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።

እንደ ብሔራዊ ሜትሮሎጂ አገልግሎት መረጃ ከሆነ በቀጣይም በቀጠናው ከባድና ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል በትንበያ መግለጹን የጠቆሙት ኃላፊው የዝናብ መጠኑ የሚቀጥል ከሆኑ በወረዳው ተጨማሪ 4 ቀበሌዎች በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገቡ ጠቁመዋል።

ዋላ ቀበሌ አካባቢ ከዋቻ ማጂ - ማጂ በሚወስደው የአስፓልት መንገድ ላይ የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ተከስቷል ያሉት አቶ መስፍን የሚመለከታቸው አካላት በፍጥነት የጥገና ስራ ካለሰሩ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ሊቋረጥ እንደሚችል ገልጸዋል።

ነገ ከዞኑ የተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው እንደሚጓዝ አቶ መስፍን ጠቁመው የባለሙያዎች ሪፖርትን መሰረት አድርጎ የዞኑ መንግስት ጊዜያዊና ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ ይመክራል ብለዋል።

እንደ ዞን ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በቅጽበታዊ ጎርፍ መጥለቅለቅ ፣ የመሬት መሰንጠቅና የናዳ ችግር ውስጥ መሆናቸውን በመግለጫቸው የጠቆሙት አቶ መስፍን በተለይ ሚዛን አማን ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

እስካሁን በሰውና በእንሳት ላይ የደረሰ አደጋ አለመኖሩን ኃላፊው ጠቁመው በሰሜን ቤንች ወረዳ ተጋላጭ በሆኑ 7 ቀበሌዎች ህጻናት ወደ ማሳ እንዳይሄዱ ማድረግ ፣ አርሶ አደሩም እንስሳትን ወደ ግጦሽ ይዞ እንዳይሄድ የቅስቀሳና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተሰራ መሆኑን በጋዜጣዊ መግለጫቸው ጠቁመዋል ሲል የቤንች ሸኮ ኮሙኒኬሽን ዘገባ ተመልክተናል።

Address

Hawassa
Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Peps or coca posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category