20/05/2026
የሰዎችን ደስታና የከተማዋን እድገት መሸከም ያቃተው አፍራሽ ኃይል ይውደም
በአንድ በኩል ለሺዎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር የኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገነባ፣ ለሕፃናትና ለደካሞች የምገባ ፕሮግራም የሚዘረጋ እና ዛሬ በጥቅሉ ገብስ ተራ ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ደግሞ ከ370 በላይ አባወራዎችንና እማወራዎችን የቤት ባለቤት አድርጎ የእንባ አባሽ የሆነ የከተማ አስተዳደር አለ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ይሄ ሁሉ መልካም ስራ ሲሰራ እንቅልፍ የሚያጣ፣ የሰዎችን ደስታና የከተማዋን እድገት መሸከም ያቃተው አፍራሽ ኃይል አለ።
ዛሬ የተረጨው የኮዬ ፈጬ እና የአራብሳ ሳይት የሱቆች የውሸት ወሬ፣ ከተማዋ እያስመዘገበችው ያለውን ተከታታይ የልማት ድሎች ለመሸፈንና የህዝብን ልብ በጥርጣሬ ለመሙላት የተወረወረ የክፋት አረር ነው። አስተዳደሩ የዜጎችን መሰረታዊ ጥያቄዎች በተግባር ሲመልስ፣ እነሱ ግን በወሬና በሃሰት ክስ ህዝብን ለማደናገር ይሮጣሉ።
ይህ የፈጠራ ዘገባ ተቃዋሚዎች ለአገርና ለሕዝብ የሚጠቅም ምንም ዓይነት አማራጭ ሃሳብ እንደሌላቸውና ስራቸው በሙሉ መልካም ስራዎችን ማጠልሸት ብቻ መሆኑን ያረጋገጠ ነው። የ370 ዜጎች የቤት ቁልፍ የመረከብ ደስታና የ20 ሺህ ወጣቶች የሥራ ዕድል ተስፋ በወሬ አይሸፈንም፤ የከተማው አስተዳደርም በእንደዚህ ዓይነት የፌስቡክ አሉባልታዎች ሳይገታ የጀመረውን የልማትና የፍትሃዊነት ጉዞ አጠናክሮ ይቀጥላል።
የከተማዋ ነዋሪዎችም የነዚህን አካላት አፍራሽ ዓላማ በመገንዘብ፣ ከወሬ ይልቅ ለመሬት ላይ እውነታዎችና ለከተማዋ ብልጽግና ትኩረት ሊሰጡ ይገባል።