04/04/2026
በቀጣይ አምስት ዓመታት፡- በሁሉም መስኮች ከተረጂነት በመዉጣት ኢኮኖሚያዊ ነጻነትን የተጎናጸፈች ኢትዮጵያን መገንባት!
ፓርቲያችን ብልፅግና በ7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በኢትዮጵያዊያን ይሁንታ መንግስት መመስረት የሚያስችል አብላጫ አባላጫ ድምጽ ማግኘት ከቻለ ሀገራችን የተሟላ ሉዓላዊነት እንድትጎናጸፍ የሚያስችላት የኢኮኖሚ ነጻነትን እንድታገኝ አበክሮ የሚሰራ ይሆናል።
ሀገራችን በሁሉም መስኮች ከተረጂነት ወጥታ፣ ያላትን ዕምቅ የልማት ዐቅም ወደ ምንዳነት ቀይራ፣ የአህጉራችንንም ሆነ የቀጣናችንን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ወደ ምትፈታበት ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ጠንካራ ሥራዎችን እንሠራለን።
ይህንን የነጻነት ጎዳና በምንጀምርበት ወቅት፣ በሌሎች ሀገራት የሚከሠቱ ችግሮች፣ የተሣሠሩ ተግዳሮቶችን እና ቀውሶችን በውስጣችን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ እንረዳለን፡ ነገር ግን ለእነዚህ ተግዳሮቶችና ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት የሚችል ዐቅም በመፍጠር፣ እየፈተኑን ያሉ ውጫዊ ተፅዕኖዎችን ለመቋቋም እንችላለን።
አብዛኞቹ የውስጥ ችግሮቻችን ከውጭ ጥገኝነት ጋር የተያያዙ ናቸው። ይህንን ውስብስብ ትሥሥር በመገንዘብ ዘላቂ መፍትሔዎችን እንቀርፃለን። በእርዳታ ላይ ያለንን ጥገኝነት እስከወዲያኛው እንዲያበቃ ለማድረግ እንሠራለን፡፡