20/02/2023
።። ።።።።። በህዝብ ነው።።።።።።።
እስከ ቀን 20/06/2015 ዓ.ም ድረስ የሚከተሉት ሁኔታዎች እንዲሟሉ እና ከነገ ቀን 14/06/2015 ጀምሮ ወደ ስራ እንዲገባ እናሳውቃለን!
።።።።።።።።።።
በወልቂጤ ከተማ ውሃ ብሎ ለወጣ ህዝብ 7 ሰዎች በፈረሰው ደቡብ ክልል ልዩ ሃይል በከባድ መሳሪያ በጠራራ ፀሃይ በጭካኔ ሲገደሉ 32 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወቃል። ይሄንን ተከትሎ ለ6 ተከታታይ ቀናት ወልቂጤ ከተማ ዛሬ ጉብሬ ምንም ህዝባዊ እንቅስቃሴ እንደቆመ ይታወቃል። ሆኖም የጉራጌ ክልል እና የፌደራሉ መንግስት እስከ ቀን 20/06/2015 ዓ.ም ድረስ የሚከተሉት ሁኔታዎች እንዲሟሉ እና ከነገ ቀን 14/06/2015 ጀምሮ ወደ ስራ እንዲገባ እናሳውቃለን=-
1ኛ . የሞቱት 7 ንፁሃን ወንድሞቻችን ገዳዮች እና እንዲገደሉ ያዘዙት ለህግ እንዲቀርቡ በግልፅ ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ! 32 የአካል ጉዳት የደረሰባቸው በህግ አግባብ እንዲታይ!
2ኛ . የፈረሰው ደቡብ ልዩ ሃይል ወጥቶ አስፈላጊ ከሆነ መከላከያ ሰራዊት እንዲገባ
3ኛ . የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳና ህዝቡ በመደበኛ ህግ እንዲዳኝ
4ኛ . የወልቂጤ ጭፍጨፋ እና አካል ማጉደል በገለልተኛ አካል እንዲታይ
5ኛ . ህዝቡ የሚያነሳቸው የውሃ እና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዘላቂነት እንዲፈታ ፈጣን የመፍትሄ ተግባራት ማሳየት!
6ኛ . ንፁሃን የጉራጌ ልጆች ማሳደድ እንዲቆም እና የታሰሩ ንፁሃን የጉራጌ ልጆች እንዲፈቱ!
ማሳሰቢያ:-
1. ከነገ ጀምሮ ከተለያየ አካባቢ ህዝቡ ጥቁር ለብሶ የሟችና አካል ጉዳት የደረሰባቸውን ቤተሰብ እንዲጠይቅ እያሳሰብን፡ ለቅሶ መድረስ ያልቻለ ባለበት ቦታ ሆኖ ጥቁር በመልበስ በሚድያ ለሞቱት ንፁሃንና ለተገፋው ጉራጌ አጋርነቱ እንዲገልፅ እንጠይቃለን!
2 . ከላይ ከ1-6 የተቀመጡ ነጥቦች እስከ የካቲት 20/2015 ተሟልቶ ምላሽ እንዲሰጥ ለፌደራሉ መንግስት እና ለጉራጌ ክልል አስተዳደር እያስጠነቀቅን ለሞቱት ነፍስ ይማር ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ህዝባችን መፅናናትን እየተመኘን የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ፈጣሪ ምህረት እንዲያወርድላቸው እየተማፀንን ከነገ ማክሰኞ ቀን 14/2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ እንዲገባ እየጠየቅን ጠቅላላ የጉራጌ ክልል አካባቢዎች ከየካቲት 20/2015 ጀምሮ ጥያቄያችን ምላሽ ካላገኘ የትግል ጥሪ እንዲጠባበቅ እያሳሰብን እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ካልተሟሉ በማንኛውም ሰዓት ጥሪ እንደምናደርግ እናሳውቃለን። ለጉራጌ ህዝብ መሰረታዊ የልማት ጥያቄና የህልውና ጉዳይ እስራት; ሞት; ስደት፡; የአካል ጉዳት ይሁን የትኛውም መሰዋትነት ለመክፈል የተዘጋጀን ሲሆን የህዝባችን ክብር በቁርጥ ቀን ልጆቹ እውን እንደሚሆን አቋማችን የፀና ነው!
የካቲት 13/2015 ዓ.ም
ወልቂጤ