08/12/2025
ታዲያ “ሙስሊም” ማለት አንዱን አምላክ በብቸኝነት ማምለክ ከሆነ እስልምና የተጀመረው መቼ ነው? አንዳንድ ስለ እስልምና እሳቤው የሌላቸው ሰዎች በነብያችን”ﷺ” የተጀመረ ይመስላቸዋል፤ ነገር ግን እውነታው እስልምና ነብያችን”ﷺ” ከመላካቸው በፊት የነበሩት ሰዎች፣ ጂንዎች እና መላእክትም ሙስሊም ናቸው፤ እንዲህ ሲባል እንደው እውርና ድንብር የሆነ ፀለምተኛ ሙግት ሳይሆን ከቋንቋ ሙግት እና ከአምላካችን ከአላህ ንግግር ተነስቼ ነው፤ ይህንን ነጥብ በነጥብ እናያለን፦
ነጥብ አንድ
“መላእክት”
በሰማያት ያሉት መላእክት ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የታዘዙ ናቸው፦
3፥83 በሰማያትና በምድር *”ያሉት ሁሉ”* በውድም በግድም ለእርሱ *”የታዘዙ”* ወደርሱም የሚመለሱ ሲኾኑ ከሓዲዎች ከአላህ ሃይማኖት ሌላን ይፈልጋሉን? أَفَغَيْرَ دِينِ ٱللَّهِ يَبْغُونَ وَلَهُۥٓ أَسْلَمَ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ طَوْعًۭا وَكَرْهًۭا وَإِلَيْهِ يُرْجَعُونَ
“የታዘዙ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “አስለመ” أَسْلَمَ ሲሆን “ሙስሊም” مُسْلِم የሚለው ቃል የመጣበት ስርወ-ግንድ ነው፣ ስለዚህ በሰማያት ያሉት መላእክት ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የታዘዙ ሲሆኑ እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፤ አይሰለቹም፦
21:19 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉም የእርሱ ነው፡፡ እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት *”እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፤ አይሰለቹም”*፡፡ وَلَهُۥ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ ۚ وَمَنْ عِندَهُۥ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِۦ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
ይህ እስልምና ውስጡ ሡጁድ ያቀፈ ሲሆን ይህም ሡጁድ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ነው፦
16:49 ለአላህም በሰማያት ያለው ከተንቀሳቃሽም በምድር ያለው ሁሉ፣ *”መላእክትም ይሰግዳሉ፤ እነርሱም አይኮሩም”*፡፡ وَلِلَّهِ يَسْجُدُ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ مِن دَآبَّةٍۢ وَٱلْمَلَٰٓئِكَةُ وَهُمْ لَا يَسْتَكْبِرُونَ
16፥50 ጌታቸውን ከበላያቸው ሲኾን ይፈሩታል፡፡ *”የታዘዙትንም”* ሁሉ ይሠራሉ፡፡ يَخَافُونَ رَبَّهُم مِّن فَوْقِهِمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ ۩
7፥206 እነዚያ እጌታህ ዘንድ ያሉት መላእክት እርሱን *“ከማምለክ” አይኮሩም፤ ያወድሱታልም፤ “ለእርሱም ብቻ ይሰግዳሉ”* ። إِنَّ ٱلَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِۦ وَيُسَبِّحُونَهُۥ وَلَهُۥ يَسْجُدُونَ ۩