04/03/2026
በሕዝብ ስም የሚነገዱ የሰላም ጠላቶች!
እነዚህ የጥፋት ኃይሎች የሕዝብ ተቆርቋሪ መስለው ቢቀርቡም፣ ተግባራቸው ግን የሕዝብን ሕልውና የሚፈታተን ሆኖ ተገኝቷል። በሕዝብ ስም እየማሉና እየተገዘቱ፣ በዜጎች ላይ ግን የሞትና የሰቃይ ጥላ እየጣሉ ይገኛሉ።
ለአንድ ሕዝብ ነፃነትና መብት እንደቆሙ ቢናገሩም፣ በተግባር ግን ያንኑ ሕዝብ ለስደት፣ ለረሀብና ለሞት እየዳረጉት ነው። ይህ የሁለቱ ሀይሎች ግልፅ ተፈጥሮ ነዉ። ሕዝብ የሚፈልገው ሰላምና መረጋጋትን ሆኖ ሳለ፣ እነዚህ ቡድኖች ግን በየቀኑ የዜጎችን ተስፋ በማጨለም የመከራውን ቀን ያረዝማሉ። ሕዝብን መውደድ ማለት የሕዝብን ሰላም መጠበቅ እንጂ ሰላማዊ ኑሮን ማናጋት አለመሆኑን እንኳን አይገነዘቡም ። የ #ሸኔ እና የ #ፋኖ የጥፋት መንገድ ለህዝባችን የሚያመጣዉ ትርፍ የለም