Arbegona W. Food System Resilience Program /FSRP

Arbegona W. Food System Resilience Program /FSRP Objective of open this page is increase product and production and to show product

26/02/2025
26/02/2025
19/02/2025

የኢትዮጵያ በምግብ ራስን የመቻል ጥረቶች

ብዙ ጊዜ አፍሪካን በዘላቂነት በዕርዳታ ላይ ጥገኛ አድርጎ በሚገልጽ ዓለም፣ ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ለመቻል ቆራጥ እርምጃዎችን በመውሰድ ይህንን ትርክት ለማስተካከል እየሰራች ነው።

በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት ባለፉት ስድስት አመታት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ፖሊሲዎችን በድፍረት በመተግበሩ የምግብ ዋስትናን ብቻ ሳይሆን የረዥም ጊዜ ራስን መቻልን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።

እነዚህ ጥረቶች ኢትዮጵያ ከጥገኝነት ለመላቀቅ እና ዘላቂ ልማትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቁ ናቸው።

እንዲህ ያለው እምርታዊ ለውጥ በውጫዊ ድጋፍ ላይ ከመተማመን ያላቀቀ በመሆኑ ትኩረትን ስቧል። ስለሆነም በአምራችነታችን እና በመረጃዎቻችን ላይ ጥርጣሬዎችን እና ትችቶችን ሊፈጥር እንደሚችል እንገነዘባለን።

አገራዊ እድገትን ለማዳከምና የልማት ጥረታችንን በተለይም በግብርናው ዘርፍ ለማጣጣል የውጭ ጥረቶች እንዳሉ እናውቃለን። ነገር ግን፣ ቁርጠኝነታችን፣ ለክብር ከሚደክሙት በርካታ ገበሬዎች ጋር ተደምሮ የምግብ ዋስትና የፖሊሲ ግብ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችን እና ለህዝባችን ህልውና አስፈላጊ ስለሆነ የማይናወጥ ነው።

የስንዴ ምርት ለማሳደግ የምናደርገው ጥረት፡ ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ወደ መቻል በምታደርገው ጉዞ የስንዴ ምርትን ዋነኛ ምሰሶ አድርጋለች። በመስኖ የሚለማ መሬት በማስፋፋት፣ የተሻሻሉ የዘር ዓይነቶችን በመጠቀምና ዘመናዊ የአስተራረስ ቴክኒኮችን ተግባራዊ በማድረግ ሀገሪቱ የስንዴ ምርቷንና ለገበያ የሚቀርበውን ምርት መጠን በከፍተኛ ደረጃ አሳድጋለች።
ይህ ስትራቴጂያዊ ትኩረት ኢትዮጵያን ከስንዴ አስመጪነት ራሷን ወደ መቻል ደረጃ በማሸጋገር የግብርና ፖሊሲዋን፣ ፕሮግራሟን እና ተያያዥ ውጥኖቿን ስኬታማነት አሳይቷል።

የኢትዮጵያ መንግስት የግብርና ምርትን ለማሳደግ የተለያዩ ውጥኖችን በመተግበር ላይ ይገኛል።

ከነዚህም መካከል፡-
• በመስኖ ላይ የተመሰረተ እርሻን ማስፋፋት - በዝናብ ላይ የነበረውን ጥገኝነትን ለመቀነስ የመስኖ ስርዓቶችን እና ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋት።

• ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ግብርና መከተል - የአየር ንብረት ለውጥን ተፅእኖ ለመከላከል ዘላቂ የግብርና ልምዶችን ማበረታታት።

• የግብርና ማሽነሪዎችን ከቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት - ከ400 በላይ የተለያየ አይነት የግብርና ሜካናይዜሽን መሳሪያዎች ከውጭ ከሚገቡት ቀረጥ ነፃ ናቸው፣ ለገበሬዎች ወጪን ይቀንሳል እና ምርታማነትንም አሳድጓል።

• የፖሊሲና የህግ ማሻሻያ - አዲስ የግብርና እና ገጠር ልማት ፖሊሲን ማስተዋወቅ፣ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅን ማሻሻል እና የኮንትራት ግብርና የህግ ማዕቀፎችን በማዘመን የወቅቱን የግብርና አሰራሮችን ማስደገፍ ተችሏል።

• የተሻሻለው የዘር ብዜት ፖሊሲ - የግሉ ሴክተር ተሳትፎን ለማሳደግ የዘር አቅርቦትና ስርጭት የቁጥጥር ማዕቀፎችን ማሻሻል፣ በዘር ብዜት እና ስርጭት ላይ ሁለገብ ተሳትፎን ጨምሮ፣ የበለጠ ተወዳዳሪ ገበያን መፍጠር።

• ተምሳሌታዊ ኢኒሼቲቮች- ሰፊ ተቀባይነት ያለው የመስኖ ስንዴ ኢኒሼቲቭ፣ የሌማት ትሩፋት እና አረንጓዴ አሻራ ሌጋሲ ኢኒሼቲቭ፣ በምግብ ራስን መቻል እና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ዋና ዋና ፕሮግራሞችን መተግበር።

• ግብርናን በክላስተር የማዘመን ስራዎችና የኤክስቴንሽን አገልግሎቶች - የክላስተር ግብርና ልምዶችን ማስፋፋት እና በዓለም ትልቁን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ፕሮግራም ማጠናከር፣ ከ60,000 በላይ የመንግስት ኤክስቴንሽን ሰራተኞች የተደገፈ የቴክኖሎጂ ማላመድና እና አተገባበርን ማሳደግ።

በስንዴ ምርት ዙሪያ መረጃ እንዴት ይሰበሰባል?

ኢትዮጵያ የግብርናውን እድገት ለመገምገም እና ስልቷን ለማጣራት ጥብቅ የመረጃ አሰባሰብ ሂደት ትከተላለች።

ይህ የሚያጠቃልለው፡-
• የመሬት ዳሰሳ ጥናቶች - በግብርና ባለሙያዎች የሚካሄደው ቅጽበታዊ መረጃን ለመሰብሰብ ነው::

• የግብርና ቆጠራ በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት - ESS ከዳሰሳ ጥናቶች በተጨማሪ በመሬት ሽፋን፣ በሰብል አይነቶች እና በምርታማነት ላይ ለውጦችን ለመከታተል የግብርና ቆጠራ ያደርጋል።

• የአስተዳደር መረጃ አጠቃቀም - አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከግብርና ሚኒስቴር እና ከሌሎች ሪፖርት አድራጊ ኤጀንሲዎች የተገኙ አስተዳደራዊ መረጃዎች እንደ የመረጃ ምንጮች ሆነው ያገለግላሉ። ነገር ግን፣ እነዚህ አሃዞች እንደ ይፋዊ የመንግስት ስታቲስቲክስ እውቅና ከመስጠታቸው በፊት በሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጥብቅ ቁጥጥር እና ማረጋገጫ ይደረግባቸዋል።

• የርቀት ዳሳሽ እና ምስል ማቀናበር - እነዚህ ቴክኖሎጂዎች በሩቅ ወይም ተደራሽ ባልሆኑ አካባቢዎች የሰብል ሽፋንን ለመከታተል ጥቅም ላይ ይውላሉ፣ ይህም የግብርና መረጃን ትክክለኛነት እና አጠቃላይነት ያሳድጋል።

ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ሌሎች ቁልፍ ጉዳዮች ላይ አስተማማኝ ስታቲስቲካዊ መረጃዎችን የማውጣት የረጅም ጊዜ ባህል ያላት ሉዓላዊ ሀገር ነች።
የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት (የቀድሞው የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ) በአፍሪካ ውስጥ ካሉ አንጋፋ እና ታዋቂ የስታቲስቲክስ ቢሮዎች አንዱ ነው። የውጭ ድርጅቶች የተለያዩ አሃዞችን ሊያቀርቡ ቢችሉም፣ የኢትዮጵያ መንግስት እንደ ሉዓላዊ ባለስልጣን ብቻ የሚመረኮዘው በአገራዊ ስርአቱ በሚመረተው ይፋዊ መረጃ ላይ እንጂ የውጭ አሃዞችን እንደ ይፋዊ ስታስቲክስ አይወስድም።
በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የእቅድ እና ልማት ሚኒስቴር የሰብል ምርት ስታቲስቲክስን ጨምሮ በተጨባጭ ሴክተር አሃዞች ላይ መረጃን የማጣራት የመጨረሻውን ስልጣን ይይዛል።

ኦፊሴላዊ የስንዴ ምርት አሃዞች

• እ.ኤ.አ. በ2022/23 ወቅት - ኢትዮጵያ 151 ሚሊዮን ኩንታል (15.1 ሚሊዮን ቶን) ስንዴ አመረተች።
o 104 ሚሊዮን ኩንታል (10.4 ሚሊዮን ቶን) በመኸር ወቅት
o 47 ሚሊዮን ኩንታል (4.7 ሚሊዮን ቶን) በበጋ መስኖ።

• እ.ኤ.አ. በ2023/24 ወቅት - ኢትዮጵያ 23 ሚሊዮን ቶን ስንዴ አመረተች።
o 12.3 ሚሊዮን ቶን በዋናው የምርት ዘመን ተሰብስቧል።
o 10.7 ሚሊዮን ቶን በበጋ መስኖ በስንዴ ውጥኖች ምርት ተሰብስቧል።

እነዚህ አሃዞች ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ላይ እያስመዘገበች ያለችውን ከፍተኛ እድገት በማሳየት በምግብ እራሷን ለመቻል ያላትን ቁርጠኝነት ያጠናክራል።

ለምንድነው የምግብ ራስን የመቻል አጀንዳ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ አስፈላጊ የሆነው?

የኢትዮጵያ የምግብ እራስን መቻል ሀገራዊ ቀዳሚ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰፊ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ማጎልበት ወሳኝ እርምጃ ነው። በምግብ ምርት ውስጥ በራስ መተማመኛን ማሳካት ጥንካሬን ያጠናክራል፣ ጥገኝነትን ይቀንሳል እና በአህጉሪቱ ዘላቂ እድገት ለማምጣት መንገድ ይከፍታል። የምግብ እራስን መቻልን ማረጋገጥ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ስትራቴጂ መሰረታዊ ምሰሶ ሲሆን ከዳርቻው ባሻገር ሰፊ እንድምታ አለው።

ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የምግብ ምርትን በማረጋገጥ ራሷን ከአለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጥ በመጠበቅ ላይ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ሀገራት የግብርና ነፃነትን ለማግኘት ያላቸውን አቅም እያሳየች ነው።

Henok Abera, [2/19/2025 11:50 AM]
ጉዞው አድካሚና ፈታኝ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ የግብርና ለውጥ ራስን ለመቻል ለሚጥሩ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች አርአያ ሆኖ ያገለግላል። ዘላቂ የግብርና እና አዳዲስ መፍትሄዎችን በማስቀደም ኢትዮጵያ አፍሪካ ራሷን የመመገብ አቅም እንዳላት እና ለመጪው ትውልድ የበለፀገ፣ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ አቅም እንዳላት እያሳየች ነው።

ይህ ኢትዮጵያ የምትኮራበት የብልፅግና ጉዞ ነው!

19/02/2025

የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትላቸውን ችግሮች ለመቋቋም ስትራተጂ ተቀርፆ እየተሰራ ነው

(አዲስ አበባ፣ የካቲት 12 ቀን 20 17 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር)

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትላቸውን ችግሮች ለመቋቋም ስትራተጂ ቀርጻ እየሰራች መሆኗን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከተለያዩ ባለድርሻና የልማት አጋሮች ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መከላከል የሚያስችል የምክክር መድረክ መካሄድ ጀምሯል፡፡

ምክክሩ “የመንግስትና የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት የላቀ ተሳትፎ ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል'' በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተካሄደ ነው፡፡

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ(ዶ/ር) የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም ከፍተኛ የንብረት ውድመትና ኢኮኖሚያዊ ድቀት ከማድረስ ባለፈ ለበርካቶች ሞትና የከፋ አደጋ መንስኤ በመሆን የዘመኑ አሳሳቢ ተግዳሮት ነው ብለዋል፡፡

ችግሩን ለመቅረፍም የባለድርሻ፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና ሌሎች አካላትን ሰፊ ርብርብ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ችግሩን በመቀነስ ረገድ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት አመታት ስትራተጂዎችን ቀርፃ ከ40 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋኗን ከ17 ነጥብ 2 ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደግ መቻሏን ሚኒስትሯ ገልፀዋል::

ሀገሪቱ ችግሩን ለመቀነስ በግብርና፣ ውሃና ኢነርጂ፣ ጤና፣ ትራንስፖርት፣ የከተማና መሠረተ ልማት ሴክተሮችን ለይቶ ወደ ስራ በመግባት የፓሪስ አየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ የ2050 የረዥም ዓመት የአነስተኛ ጋዝ ልቀት ስትራተጂ ነድፋ እየሰራች እንደምትገኝ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።

#ከማምረትበላይ

----------------
ስለግብርና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፦
ድረ-ገጽ፦ www.moa.gov.et
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/MoAEthiopia
ዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/MoAEthiopianews
ቲዊተር፦ https://x.com/MoA_Ethiopia

19/02/2025

የወሩ ሰብል- በቆሎ🌽

የአትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት በሚተገበረዉ የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮግራም 11 ቅድሚያ የሚሰጣቸው ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጓ ይሰራል።በዛሬዉ የወሩ ሰብል ማስተዋወቂያችን ከነዚህ ትኩረት ከተደረገባቸዉ ምርቶች ዉስጥ 🌽በቆሎን መርጠን እናቀርባለን፡፡ በቆሎ በኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ሀገራዊ ኢኮኖሚ ለማሳደግ ወሳኝ ሰብል ነው። በሰብል የአርሶ አደር ምርት ክላስተር ፕሮጀክት አማካኝነት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች በተመረጡ የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮግራም በሚተገበርባቸዉ ክልሎች ማለትም በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኙ በቆሎ አምራች አርሶ አደሮች በቆሎን አምርተዉ ከፍጆታ ባለፈ ለገበያ እንዲያቀርቡ ድጋፍ እያደረገ ነው። 🌽

በቆሎ በምግብ ራስን መቻል እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ ካለው ጉልህ ሚና አንፃር በኢትዮጵያ በአመራረትም ሆነ በምርታማነት ቀዳሚ ሰብል በመሆኑ ቅድሚያ የሚሰጠዉ ነዉ። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች በቆሎ የሚያመርቱ ሲሆን 77.4% የሚሆነው ምርት በአርሶ አደሩ ቤተሰብ ለምግብነት ይዉላል። በቆሎ በኢትዮጵያ ውስጥ በጣም ርካሹ የካሎሪ ምንጭ ሲሆን ይህም የአገሪቱን የነፍስ ወከፍ የካሎሪ መጠን 20.6 በመቶውን ይይዛል። በቆሎ ከምግብ ዋስትና ባለፈ የሀገር ውስጥ መጠጦችን ለማምረት ያገለግላል፤ ቅጠሉም ለእንስሳት መኖነት የሚያገለግል ሲሆን ግንዱም ለግንባታ እና ለማገዶነት ይውላል። በቆሎ በስነ ምግብ ይዘቱ በካርቦሃይድሬት፣ ፕሮቲን፣ ዘይት፣ ፋይበር እና ቤታ ካሮቲን የበለፀገ ሲሆን ቢጫ በቆሎ የፕሮቪታሚን ኤ ዋና ምንጭ ነው። 🌽

በኢትዮጵያዊያን አመጋገብ ውስጥ ዋነኛ የሆነው 🌽በቆሎ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የምግብ አቅርቦትን ለማሻሻል ወሳኝ ሚና ይጫወታል። የተጠበሰ እና የተቀቀለ የበቆሎ እሸት በከተማም ሆነ በገጠር በስፋት በመስፋፋቱ ለሴቶችና ለወጣቶች የስራ እድል ይፈጥራል። በኢኮኖሚ ረገድ በቆሎ ከፍተኛ የገበያ ተደራሽነት ያለው ሲሆን ለአርሶ አደሮች እንደ ዋና የገቢ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል። በተጨማሪም ሌሎች የሰብል ዘሮችን በመተካት እና ለእንስሳት መኖ ምርት እንደአስፈላጊ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ያገለግላል።

🌽የአትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ድጋፍ፦

የበቆሎ ምርትን፣ ምርታማነትን እና የንግድ ልውውጥን ለማጎልበት የአትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮግራም በሚተገበርባቸዉ ክልሎች ውስጥ በርካታ ተግባራዊ ድጋፍ አድርጓል።

🌽አርሶ አደሮችን በአርሶ አደር ምርት ክላስተር ማደራጀት፦ አጎራባች መሬት ያላቸው አርሶ አደሮች በቡድን በመሰባሰብ ዕውቀትን ለመለዋወጥ፣ ግብዓቶችን በመግዛት እና ምርታቸውን በብቃት ለገበያ ለማቅረብ ማዘጋጀት።

🌽የአቅም ግንባታ መርሃ ግብሮች፦ አርሶ አደሮችን፣ የግብርና ባለሙያዎችን እና የልማት ጣቢያ ሰራተኞቸን ሁሉንም የበቆሎ ቴክኖሎጂዎችን በብቃት እንዲጠቀሙ ማሰልጠን።

🌽የግብርና ግብአቶችን ማመቻቸት፦ አርሶ አደሮችን በተለያዩ የግብአት አቅርቦት ስርዓቶች እንደ የግብርና ግብዓት የኩፖን ሸያጭ ሥርዓት ፣ ቀጥታ የዘር ግብይት እና የግብርና ግብዓት አቅርቦትና አገልግሎት ድጋፍ ማድረግ።

🌽በምርት ላይ የተመሰረተ የእሴት ሰንሰለት ጥምረት መፍጠር፦ ቁልፍ ባለድርሻ አካላትን በአንድ ላይ በማሰባሰብ የአርሶ አደር ምርት ክላስተርን በእሴት ሰንሰለቱ ውስጥ መደገፍ።

🌽የንግድ ሥራ አመራር ስልጠና መስጠት፦ የአርሶ አደሮችን እና የልማት ጣቢያ ሰራተኞችን በፋይናንስ እውቀት እና በገበያ ተኮር ክህሎት ማጎልበት።

🎯 የዲጂታል ግብርና አገልግሎቶችን መጠቀም፡-

📳8028 የአርሶ አደሮች አገልግሎት መስጫ የስልክ መስመር ፦ አርሶ አደሮች ነፃ የግብርና ምርት ቴክኖሎጂ መረጃን በቀጥታ ጥሪ መልእክት ማግኘት ይችላሉ።

📳6077 ሀገር አቀፍ የገበያ መረጃ ስርዓት፦ በአርሶ አደር ምርት ክላስተር የተደራጁ አርሶ አደሮች የገበያ ዋጋ መረጃን በነጻ ጥሪ ማግኘት ይችላሉ።

🌽ድጋፍ መስጠት፦ የግብርና ማሽነሪዎችን ማሰራጨት፣ የተሻሻሉ የድህረ ምርት አያያዝ ቴክኖሎጂዎች እና በአርሶ አደር ምርት ክላስተር ለተደራጁ አርሶ አደሮች የቢሮ መሠረተ ልማት መደገፍ።

በአትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የተደረገው ድጋፍ 🌽በበቆሎ አምራች አርሶ አደሮች ኑሮ ላይ ከፍተኛ መሻሻሎችን በማምጣት ለሀገራዊ ኢኮኖሚ አስተዋፅዖ አድርጓል። በተለይም በ2016 የበጀት ዓመት 835,400 የበቆሎ አምራች አርሶ አደሮችን በ30,800 የአርሶ አደር ምርት ክላስተር በማደራጀት ከ40.6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርት ማምረት ተችሏል። ከዚህ ውስጥ 10 ሚሊዮን ኩንታል ትርፍ ምርት የተሸጠ ሲሆን 30.8 ቢሊዮን ብር በማስገኘት የበቆሎ ምርት በአርሶ አደሩ ኑሮ እና በአገራዊ ኢኮኖሚ እድገት ላይ ያለዉ አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል። 🌽

Ministry of Agriculture - Ethiopia
Ethiopian Institute of Agricultural Research - EIAR
Ethiopian Cooperative Commission

ለበለጠ መረጃ ፡
Facebook:
https://www.facebook.com/EthiopiaATI
Twitter or X:

LinkedIn:
https://www.linkedin.com/posts/ethiopianata
YouTube:
www.youtube.com/
ይወዳጁን፡፡

  Programenni   woradi Xooggu ollii giddo 15hectaare laash*tanno waayi projeette( ganda) prograamenke wo'ma woce dandiit...
06/02/2025

Programenni woradi Xooggu ollii giddo 15hectaare laash*tanno waayi projeette( ganda) prograamenke wo'ma woce dandiite loose daganke gorsu loosinni horameeyye ikkitanno gede wayi injo qixxeesite loosidhe galtinno daganke sagaletenni umonsa dandiitanno gede wixu irkono assine arri(gorsu) looso konni garinni loosiinsanni afamemmo xaano sunfeemmo!

Arbegoonu woradi FSRP irkonni daganke sagalete umo dandiisisate hawadi xeena calla agadhitukki Arrihu Gorsu Loosinni Maa...
24/01/2025

Arbegoonu woradi FSRP irkonni daganke sagalete umo dandiisisate hawadi xeena calla agadhitukki Arrihu Gorsu Loosinni Maatete Jireenya buuxisiisate Qasiisote Dinnichu kaasho kayisinsanna Bexxo Uraago qasiisora.

Address

Arbegoona
London

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arbegona W. Food System Resilience Program /FSRP posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category