Muhaba kedir husen

Muhaba kedir husen zena

11/06/2025

ነብዩ ሙሀመድ ﷺ አባታቸውን ከመወለዳቸው በፊት ነበር ያጡት። ውዱ ነብያችን ﷺ በበረሃ ሃገራቸው እናታቸውን ገና በ6 አመት ሳሉ ነበር ያጡት። እናታቸው በህመም ሳሉ በአይናቸው አይተዋል፤ በዛ ልጅነታቸው ይህን አለም ለቃ ስትሄድባቸው ከጎን ሆነው መስክረዋል። አያታቸው ያሳድጓቸው ጀመር። እስከሚችሉት ድረስ ፍቅርና እንክብካቤን አድርገውላቸዋል። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ በ8 አመት ሳሉ አያታቸውንም አጡ። ባለቤታቸው አለም ላይ ካሉ ሰዎች እርሳቸው ዘንድ ተወዳጅ ነበረች። ነገር ግን በከባድ የፈተና ወቅት እርሷንም አጥተዋል።

8አመት ከሞላቸው በዃላ በአጎታቸው ስር ሆኑ። መካ ላይ አጎታቸው ለነብዩ ﷺ ከለላቸው ነበሩ። ነገር ግን ከነብዩ በፊት አለፉ። እንደ አባት ሆነው ያሳደጓቸውን አጎታቸው አሰቃቂ ሞት በአይናቸው አይተዋል። ልባቸው በሀዘን ተሰብሯል። እንደ እናት ሆና ያሳደገቻቸው አክስታቸውን በእጃቸው አፈር አንስተው ቀብረዋል።

ልጆቻቸው ገና ልጅ እያሉ ነው የሞቱባቸው። 4 ወንድ ልጆቻቸውን በህይወት ሳሉ ቀብረዋል። የተባረከ አይናቸው ብዙ አንብቷል። የሚወዷቸው ባልደረቦችና አብሮ አደጎቻቸው ሲሰቃዩና ህይወታቸው ሲያልፍ በህይወት ሳሉ አይተዋል። በድር ዘመቻ ሄደው ሲመለሱ ሴት ልጃቸው ወደ አሄራ መሄዷን ነበር የተበሰሩት። ህይወት ትቀጥላለች። ሌላ ሁለት ሴት ልጆቻቸውን በተባረከ እጃቸው አፈር አልብሰዋል። ምን ያህል ከባድ ነው? ምን ያህል ጥንካሬ ነው?

ይህ ሁሉ ሆኖ ሳለ አንድ ሰሃብይ ስለርሳቸው ሲናገር "ነብዩ ሙሀመድን ﷺ ፈገግታ ተለይቷቸው አይቼ አላውቅም" ብሎ ነበር። ሰለዋቱ ላሂ ወሰላሙ አለይህ!! ምንኛ ያማረ መልካም ባህሪ ነው?
የርሳቸውን ፈለግ የተከተለ በሙሉ አላህ ባጣነው ይተካልን ሰብሩንም ይለግሰን እላለሁ🙏🙏

28/04/2025

Address

Wukiro Kabale
Awassa
WA

Telephone

+251938192720

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Muhaba kedir husen posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share