Jamal Abdalla

Jamal Abdalla Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Jamal Abdalla, Grocers, Dire, Addis Ababa.

02/06/2026
02/06/2026

ኢትዮጵያ መለህቲ!

02/06/2026

Itoophiyaan Injifattee Jirti!

02/06/2026
02/06/2026

ኢትዮጵያ መርጣለች!
#ኢትዮጵያመርጣለች

02/06/2026

ከሀረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

የሀረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከ7ኛው ክልላዊና ሀገራዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ መግለጫ ሰጥቷል።

ምክር ቤቱ በመግለጫውም በ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫው ሂደት ወቅት የታዩ አዎንታዊ ጅምሮችን ይበልጥ በማጠናከር የምርጫውን ሰላማዊነት፣ ዲሞክራሲያዊነት፣ ነፃና በሕዝብ ዘንድ ታማኒነቱን ማጠናከር ይገባል ብሏል።

የጋራ ምክር ቤቱ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕዝቡን ውሳኔ እና ድምፅ እንዲያከብሩ፣ ደጋፊዎቻቸውን ወደ ሰላም፣ መከባብር እና ሕጋዊ አሠራር እንዲመሩ እና ማንኛውንም ልዩነት በውይይት እና በሕግ ማዕቀፍ እንዲፈቱ ጥሪውን አቅርቧል።

የምርጫው ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ መሠረት ተረጋግጦ እስከሚገለፅ ድረስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትዕግሥትና በኃላፊነት ስሜት እንዲቀሳቀሱ ጠይቋል።

ከምርጫ በኋላም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የምክክር እና የመግባባት ባህል እንዲጠናከር ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና በጋራ እንደሚሰራ ነው ያስታወቀው።

ማንኛውም ቅሬታ በሕጋዊ መንገድ ብቻ መፍታት እና በሰላምና በብሔራዊ ጥቅቅም ጉዳይ ትብብርን መሠረት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ተመላክቷል።

የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይት እና በዴሞክራሲያዊ ሂደት የመፍታት ባሕላችንን ማጠናከር እና የትብብር እና የፉክክር ሚዛንን በማስጠበቅ የመደብለ ፓርቲ የዲሞክራሲ ባሕልን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን የጋራ ምክር ቤቱ በሰጠው መግለጫ ገልጿል።

02/06/2026

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ድምጹን በመስጠት ለዲሞክራሲዊ ግንባታ አስተዋጽዎ አድርጓል የሀረሪ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽን

የሀረሪ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽን በትላንትናው እለት የተካሄደውን 7ኛው አገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

በሀረሪ ክልል በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ የክልሉ ፌዴሬሽን አመራሮች ጨምሮ 250 የሚጠጉ ወጣቶች በምርጫ ታዛቢነት ተሳትፈዋል።

የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ወጣት ረስተም ኡመር እንደገለጹት ፌዴሬሽኑ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የምልከታ ስራዎችን አከናውኗል።

በዚህም ምርጫው ፍፁም ሰላማዊና ነጻ ሆኖ መጠናቀቁን ተለያዩ አካላት የተሰበሰቡ መረጃዎች ያረጋገጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በተገኘው መረጃ መሰረትም ዜጎች የወደዱትንና የፈለጉትን የፖለቲካ ፓርቲ ያለ ምንም ጣልቃ ገብነትና ተጽዕኖ ሳይኖር በነጻነት መምረጥ መቻላቸውን አረጋግጠናል ብለዋል።

የክልሉ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ፣ ይበጀኛል ያለውን ፓርቲ በሰለጠነ መልኩ በድምጹ በመምረጥ ለዲሞክራሲ ግንባታ ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ወጣት ረስተም ኡመር ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የምርጫው ሂደት በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ ፌዴሬሽኑ ምስጋናውን አቅርቧል።

Address

Dire
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jamal Abdalla posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category