Yezena Yezena

Yezena Yezena አለ ይቻላል

የፎቶ ፓለቲካ ለዶላር መለመኛ ለማንኛውም የጽንፈኛው ፓለቲካ ፎቶ በመነሳት ዶላር መለመን ነው። እንጂ ምንም የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት የመመከት አቅም የለውም። ስንት ተደራጀው ያለው ወ*?...
23/06/2023

የፎቶ ፓለቲካ ለዶላር መለመኛ

ለማንኛውም የጽንፈኛው ፓለቲካ ፎቶ በመነሳት ዶላር መለመን ነው። እንጂ ምንም የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት የመመከት አቅም የለውም። ስንት ተደራጀው ያለው ወ*?ያኔ እንኳን ቀምሶ ሰላምን በመምረጥ ቁጭ ብሏል።

አላማ የሌለው ትግል ይዘው በአማራ ህዝብ ላይ የማይጠቅም የግል ፓለቲካ እየሰሩ ያሉትን ጽንፈኛ እስከ መጨረሻ ድረስ መታገል ይኖርብናል።

አማራ በአሁኑ ሰአት የትግል ስልቱን በማሻሻል ጥያቄዎቹን ለኢትዮጵያ ህዝብ እያስረዳ ባለበት ሰአት የአማን ህዝብ የዶላር መለመኛ ማድረግ የሚፈልጉ ሚዲያዎች ጽንፈኛ ሀይሎች በማይጠቅም የትግል ስልት ህዝቡን እረፍት እየነሱት መሄድ ጀምረዋል። አንድ ሜትር እንኳን የአማራን ትግል ውጤታማ የማያረጉ ጽንፈኛ ሀይል ሁላችንም መታገል አለብን። ዘመኑ ሰለተቀየረ

09/02/2023
30/01/2023

ከ27 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ለሚገነባው የዘንገና ሐይቅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ።

በምክትል ርእሰ መሥተዳደር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ ሰማ ጥሩነህ (ዶ.ር) እና የክልሉ ከፍተኛ መሪዎች በተገኙበት የዘንገና ሐይቅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ለማስጀመር የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ግርማ የሺጥላ፤ መንግሥት የትምህርት ጥራትን ስብራት ለመጠገን በሚያደርገው ጥረት የአከባቢው ተወላጆች ምሁራንና አመራሮች ለትምህርት ጥራት ትኩረት በመስጠት ዘንገና ሐይቅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሠረተ ድንጋይ በማስቀጣቸው የአማራ ክልል መንግስት ልዩ ክብር መኖሩን ተናግረዋል።

የዘንገና ሐይቅ ጥልቀቱ በውል እንደማይተወቅ ሁሉ ዘንገና ሀይቅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ የሚመሩ ተማሪዎች እንደሀይቁ ጥልቅ እውቀት ያላቸው ምሁራን እንዲሆኑ አቶ ግርማ የሺጥላ አሳስበዋል።

የአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ ዶክተር ሰማ ጥሩነህ በበኩላቸው፤ የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ማኅበረሰብ በክፉ ጊዜ ዘማች በሠላም ጊዜ አምራች መሆኑን ጠቁመው በከሳ ቸውሳ ቀበሌ ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ባለመኖሩ በቀበሌ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች እየተቸገሩ በመሆኑ ማኅበረሰቡንና ተወላጆችን በማስተባበር ዘንገና ሀይቅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት መሠረተ ድንጋይ በማስቀመጣቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የአዊ ኮሙኒኬሽን መረጃ እንደሚያሳየው፤ በትምህርት ቤቱ ግንባታ በርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉ መሆኑን የገለፁት ዶክተር ሰማ፤ ግንባታው እስኪጠናቀቅ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አስተላልፈዋል ።
(አሚኮ)
•~•~•
"የጎሃ ቃልኪዳናችን የከፍታችን ልክ ፤ ቃላችንን ፈፅመን ከፍታው ላይ እንገናኝ"
~~~
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ትዊተር :- https://twitter.com/AppAmhara?s=09
ዩቲዩብ :- https://youtube.com/channel/UCxQ5MOnm-YH514Qdta0Kysg
ቴሌግራም ፡-https://t.me/appamhara01

14/01/2023

በኢትዮጵያ ዓመታትን ጠብቀው የሚከበሩ ሀይማኖታዊ በዓላት ከእምነት ፋይዳቸው ባለፈ በውስጣቸው በያዙት መስህባዊ ተፈጥሮ ምክንያት በርካት የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎችን ይስባሉ። ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ደግሞ የጥምቀት በዓል ነው።

የጥምቀት ዋዜማ ከተራ ይባላል፡፡ የከተራ ዕለት ጥር 10 ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በሚሰማው የደውል ጥሪ ታቦታቱ፤ የተለያዩ ህብረ ቀለማት ያላቸው አልባሳት በለበሱ ህዝበ ክርስቲያን ታጅበው ጉዟቸውን ወደ ጥምቀተ ባህር ያደርጋሉ፡፡

በከተራው ዕለት ድንኳን ተተክሎ፣ ዳሱ ተጥሎና ውኃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ፤ ታቦተ ህጉ የሚንቀሳቀስበት ሰዓት ሲደርስ የየቤተ መቅደሱ ታቦታት በወርቅና በብር መጎናፀፊያ እየተሸፈኑ፤ በተለያየ ህብር በተሸለሙ የክህነተ አልባሳት በደመቁ ካህናትና መስቀል በያዙ ዲያቆናት ከብረው፣ ከቤተ መቅደስ ወደ ጥምቀተ ባህር ቦታ ለመሄድ ሲነሱ መላው አብያተ ክርስቲያናት የደውል ድምፅ ያሰማሉ፡፡

ምዕመናንም ከልጅ እስከ አዋቂ በአፀደ ቤተ ክርስቲያን እና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ እንደሚባለው ያማረ ልብሳቸውን ለብሰው በዓሉን ያደምቃሉ፡፡

ታቦታት ከቤተ መቅደሳቸው ወጥተው በህዝበ ክርስቲያኑ ታጅበው ማደሪያ ቦታቸው ይደርሳሉ። በዚያን ጊዜ ዲያቆናትና ቀሳውስት በባህረ ጥምቀቱ ዙሪያ ሆነው ከብር የተሰሩ መቋሚያና ፅናፅል እንዲሁም ከበሮ ይዘው በነጫጭና በወርቅ ቀለም ባሸበረቁ እጥፍ ድርብ አልባሳት አምረውና ተውበው፤ የክርስቶስን የጥምቀት ታሪክ የሚያወሱ ወረብና መዝሙሮችን ጣዕም ባለው ዜማ ያቀርባሉ።

ሌሊቱን በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ፕሮግራሞች ታጅቦ ያድርና ስርዓተ ቅዳሴው ይፈፀማል፡፡ በጥምቀተ ባህሩ ወንጌላት ከተነበቡ በኋላ ባህረ ጥምቀቱ በብፁዓን አባቶች ተባርኮ ለተሰበሰበው ህዝበ ክርስቲያን ይረጫል፡፡ ለዚህ በዓል ህዝበ ክርስቲያኑ ልዩ ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ ምክንያቱም በዓሉ እየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ የተጠመቀበትን ተምሳሌት በማሰብ ስለሚከበር፡፡

ህዝበ ክርስቲያኑ ይህንን በዓል በአንድነት ያከብሩታል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ህዝብን ያቀራርባል፤ የመረዳዳት ባህልንም ያሳድጋል፡፡

የጥምቀት በዓል በሁሉም የአማራ ክልል አካባበዎች በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት አንዱ ነው፡፡ በጎንደር፣ ላሊበላና ባህር ዳር በዓሉን ለማክበር የተለያዩ ሀገር ዜጎች፣ ዲፕሎማቶች፣ አምባሳደሮችና ከፍተኛ ባለስልጣናት እንዲሁም የቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ከበዓሉ ቀን ቀደም ብለው ተገኝተዋል፡፡

የጥምቀት በዓል በአይነትና በመጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ለአማራ ክልል የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሎታል፡፡ ስለዚህ በዓሉ በሰላም ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ተገቢውን ትኩረት ልንሰጠው ይገባል፡፡

•~•~•
"የጎሃ ቃልኪዳናችን የከፍታችን ልክ ፤ ቃላችንን ፈፅመን ከፍታው ላይ እንገናኝ"
~~~
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ትዊተር :- https://twitter.com/AppAmhara?s=09
ዩቲዩብ :- https://youtube.com/channel/UCxQ5MOnm-YH514Qdta0Kysg
ቴሌግራም ፡-https://t.me/appamhara01

13/01/2023

ይህን አገር ማዳን የምንችለው በህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት፤ በእኩልነት እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አንድነት በመገንባት ነው፤

ክቡር አቶ ግርማ የሽጥላ
የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ አባል

•~•~•
"የጎሃ ቃልኪዳናችን የከፍታችን ልክ ፤ ቃላችንን ፈፅመን ከፍታው ላይ እንገናኝ"
~~~
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ትዊተር :- https://twitter.com/AppAmhara?s=09
ዩቲዩብ :- https://youtube.com/channel/UCxQ5MOnm-YH514Qdta0Kysg
ቴሌግራም ፡-https://t.me/appamhara01

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yezena Yezena posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category