08/01/2026
!!
!!
#በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በአልቾ ውሪሮ ወረዳ የሚገኘው የኩተሬ ማህበረሰብ ራሱን በራሱ የወረዳነት ጥያቄ ካቀረበ ሁለት አስርተ ዓመታትን (20 ዓመታት) አስቆጥሯል።
#ይህ ማህበረሰብ ጥያቄውን በጉልበት ሳይሆን በህግ፣ በሁከት ሳይሆን በሰላማዊ መንገድ፣ በግፍ ሳይሆን የሚገባውን መብት መሰረት አድርጎ ለሚመለከተው የመንግስት አካል ሁሉ አቅርቧል። መስፈርቶችን ሁሉ አሟልቶ "ታገሱ" እየተባለ ለ20 ዓመታት ያህል ቃል እየተገባለት ቆይቷል። አሁን ግን ትዕግስቱን ጨርሷል።
#ልማትን በቅርበት ለማግኘት፣ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና የዴሞክራሲ መብትን ለመጠቀም የቀረበው የወረዳነት ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። መንግስት የገባውን ቃል እንዲያከብርና የኩተሬን ህዝብ ድምጽ እንዲሰማ እንጠይቃለን!!
#የኩተሬ የወረዳነት ጥያቄ የፍትህና የልማት ጥያቄ ነው!
#20 ዓመት የታገሰ ህዝብ ዛሬ ምላሽ ይፈልጋል!
#መስፈርቶችን አሟልተናል፣ ምላሹን እንሻለን!
#ለኩተሬ ወረዳነት እውቅና መስጠት ለሰላምና ለልማት እውቅና መስጠት ነው!
#የገባችሁት ቃል በተግባር ይተርጎም!
#የህዝብ ድምጽ የዴሞክራሲ መሰረት ነው፤ የኩተሬ ድምጽ ይሰማ!